ምጽአትBy: cosmos-2000, June 2009 ካገሩ የወጣ አገሩ እስኪመለስ...መባሉን እያወቀችያልፍልኛል ብላ ሕፃን ልጇን አቅፋ ስደትን መረጠች::መከራ በዝቶባት መምረጥ ተገደደች ካለመኖር መኖርከሰው ላይ ሰው ጭነው በታንኳ ታጭቃ ወደ ውጭ ስትበርሜዲትራንያን ግብር አስከፈለ ቀንቶ በቀይ ባሕር::ወያኔን ቢጠሉ ሄዱ ወደ ስደት ውሃው ይብላን ብለውከሞት እየሸሹ ወደሞት ይጓዟል ይሏችኋል ይህ ነው::ወጣት አበቦችም በጠራራው ፀሐይ ተሽጠው ሲሄዱእንደ ሰው ሰው መሆን አቃታቸውና ስንቶች ተዋረዱ::ወተሽ እንዳትጠፊ አቤት እንዳትይም በሩን ቆልፎብሽምግብ አዘጋጅተሽ ደክሟታል ሳትባይ ዕቃውን አጣጥበሽወጥቶ ለመጫወት ከጓደኞችሽ ጋር እረፍት የት አግኝተሽ::የባርነት ኑሮ እንድትኖሪ አውቃለሁ የቁም ስቃይ አይተሽለማይቀረው ሞቱ መገላገል ፈለግሽ ሕይወትሽን አጥፍተሽ::ተቆርቋሪ ቢያጡ በአራቱ ማዕዘናት ሄዱ ተሰወሩበየደረሱበት ምግባረ ብልሹ ተብለው ተጠሩ::ለነፃነት ሞተው ተተኪውን ትውልድ እንዳላስከበሩልጅማ አላወጡም ተወልዶም ይሆናል ይታያል ተግባሩ::እንኳን ለራሳቸው ለአፍሪካ ነፃነት ለትግል ቀስቅሰውታሪካቸውማ በዓለም ተመዝግቧል አንድም ሰው አይክደው::ለጥቁሮች ማጎሪያ ቅኝ ገዢዎቹ እስርቤት ሲሠሩቅኝ ገዢው ሳይገባ ኢትዮጵያውያኑ እየገቡ ታጎሩእንዳርበኞች ቢሆን ይታያቸው ነበር ዱሩ ሸንተረሩ::በርከት ያሉ ናቸው የነፃነት ትግልን በጧት የጀመሩማቸነፍ ማለትን ሳያውቁ ተጉዞው በውር በድንብሩሃቅን ስለያዝን ለማቸነፍ በቃን የሚሉት ዲስኩሩጩኸትማ ሰማን የወያኔዎችን ሃሰት ሲናገሩ::ሃቅማ ቢይዙ ፀሃይ እየወጣች ብርሃን እናይ ነበርአንደበት ተዘግቶ ታስረን ተባረርን በራሳችን አገርዘረኛና አጃቢው ሲሆኑ አየናቸው ምሰሶና ማገር::ላንድነት የሚቆም በመስዋዕትነቱ አቅርቦና ስቦመታመን በተግባር መታፈር በከንፈር ብሎ ተረባርቦበሃቅ እየዘገቡ ለጋራ ጥቅማችን ሥራውን መዝግቦከወረደው ጥበብ “አንድ ሰው አስቦ አንድ በሬ ስቦ”ልቦና ለሰጥው ፍንትው ይልለታል ከፊታቸው ቀርቦ::ሹክ ብላቸውም መልስ አልሰጠኝ አሉ በዝቶ ውዥንብሩበማኝ ፊት ብናገር ብናርፍ ይሻለናል ብለው ተሰወሩፈርተን ነው ካላሉ እኛ የማይገባን ምንድን ነው ሚስጥሩ?እናብር ስንለው እኔ ተቀብሬ መገኘቱን ይሻል ካዘኑ ከቀብሩዝምታ ወርቅ ነው መባል ይቁም በቃ በርትቷል ችግሩ::በሰከሩ ቁጥር ሚገድሉን ከሆነ እስቲ ምቱ መላዓይናፋር ይመስል ዝምታን ስትመርጡ ሕዝቡ እየተቆላሂዱ ተተፍተፉ እንዲወጣላችሁ የሰው ዓይነ ጥላ::ስልቱ ገድሎ ማዳን ግንባር ቀደም ሆኖ ካሳየን አጉልቶአነጣጥረህ ምታ ደግ ነህ አልተባልክ አድሮና ሰንብቶ::የሚጽፍም ይጻፍ ሸንጎ ፍጠሩና እስቲ ተማከሩአትሸፋፍኑት ይታወቅ ሰው-በላው ሰይጣናዊ ምክሩ::ዝምታ ወርቅ ሚሆን:- ተስፋ ሲደርቅ ነው ወይስ ሲለመልም?ተስፋማ ይለመልም ነጣጣይ ዘረኛ ካገር እንዲል እልም::ተስፋንማ ሥሩ ጥቂት በጥቂቱ እኛም ደጀን ሆነንዕውን የሚሆነው ግፈኛ ተመቶ አገሩ አገር ሲሆን::ምኞታችንን ገድሎ ስጋችን ጨረሰው እየዋለ እያደረአለመያዝ ደጉ አለመቀደም የተያዘው ሁሉ እንደወጣ ቀረ::የጸሃፊን ብዕር በጉልበት አባሮ ሃሳብ እየቀበረጅሉም ስላልገባው ግፈኛውን አምኖ ሕይወቱን ገበረ::ያውም በኛው አገር አሠሩን ገሰሱን እሥረኛ ይበላልየሚቀምሰው አጥቶ ሕዝቡ በየተራ በረሃብ ክልትው ይላልየሕዝባችንን ኑሮ ዓይናችን ዓይቶታል ልቦናችን ያውቃልእንዲያው የለየለት ቁርጡ የታወቀው የእሥረኛው ይሻላል::ትምህርት ቤት ገባሁ ገጠሩንም አየሁ ዙሬ ተዟዙሬአብሮ መኖር ተማርኩ ትዳርን መስርቼ ሥራም ተቀጥሬውቅያኖስ አየሁኝ ባሕር አቋርጨ ውጭ አገርም ኖሬአገር በማጥፋቱ ወያኔን የሚያስንቅ አጣሁኝ መርምሬ::ነግደው:- ለምነው:- በተገኘው ገንዘብ አጋዚን ተመቸውበገደሉ ቁጥር ብሶባቸው መጡ ደም እየጠማቸውየወገናችን ደም መጠጣት ሲበዛ ስካሩ አዞራቸው::ለማምነው ሲያመጡ በገንዘቡ ብዛት ጎረቤት ወረሩአማራም አልቀረ ኦሮሞ ሶማሌ አኝዋክና አፋሩሲዳማና ትግሬው የከታማው ነዋሪ እንዲሁም ገጠሩበእብሪት ተወጥረው ማን አለብኝ ብለው አገር መነጠሩ::ከሃዲና ባንዳ አገር አከሰረ ባንኩንም ዘረፈሚቆረቆር መስሎ የልቡን እየሠራ ፍትሕ አዛነፈ::ታሪክን ሰርዞ ለሰንደቃላማው የግል ትርጉም ሰጥቶበመዝሙር ሲያጅቡ ጆሯችንን ደፈንን ጩኸቱ በርትቶቢውለበለብ ቅሉ በልብ አናቅፈውም የኛን ትርጉም ትቶ::እራሱ አጽድቆ እራሱ ከልክሎ መብትን አፈነናአየር ደመናውን ሰማዩን ለማየት ቀና በሉ አለናካለእኔ በስተቀር ከአናታችሁ በላይ ከቶ ማን ቆመናዝናቡም የኔ ነው ውሃ የቋጠረን ማንሳፍፍ ደመና::በነጎድጓድ ድምጤ ፍጡራንን ሁሉ ማኖር አሸብሬመብረቁን ሳባርቅ ስሃሊለነ ብለው ይስገዱ ወደ እግሬከዋክብትን እዩ የዘራኋቸውን ወጥሬ ገትሬጨረቃንም ሰጠሁ ማማረራችሁን ስለሰማሁ ወሬ::የሁሉም ማዕከል ፀሓይማ እኔ ነኝ እምቦለሌ ማዞርምንም ሳላዛንፍ ጨለማና ብርሃን ወቅቱን ማቀያይርሙቀት እየሰጠሁ እፅዋት ለምልመው ሚበላ የምቸር::ይህን ሁሉ አድርጌ ሊፈትነኝ መጣ ጉልበቴ ተንቆአቅሜን ላስመሰክር ከአፋር በሚነሳው የሽምጥ ሸለቆአለቱን ብረቱን አንድ ላይ አቅልጨ ገድል ልሥራ ብዬእንደ ማንዳ ሃራሮ እሳተ ጎመራ ወደላይ ገንፍዬእንደ ዳላፊላ የእሳት አለሎውን አውጥቼ አንቀልቅዬምድርን ያለምሰሶ ሰማይን ያለ ባላ ቀጥ አርጌ አቁሜጉልበቴን ፈርታችሁ እንድትሰግዱልኝ ነው ይህ ሁሉ ድካሜ::ልባችሁ ሸፍቶ ጌታ ሆይ ብላችሁ መች እኔን ጠራችሁ?ከእኔ በላይ ላሳር ክብሬን አትጋፉ አሁንስ ገባችሁ?ቁጣዬ በርትቶ ደጋግሜ ሞከርኩ ክንዴን ላሳያችሁ::ለምድራዊ ስልጣን ቀናዒ መሆኔን ያዳም ዘር እንዲያውቅዕድሜዬ ሚረዝመው በእኔ ሥር ሲውል ነው ያገሪቱ ወርቅ::ሁለቱን እሴቶች ከመዳፌ አውጥቶ የሚወስድ ከመጣየጦር ሠራዊቴ እርምጃ ይወስዳል የለብኝም ጣጣ::ቢረገም ነው እንጂ ሰይጣን መልአክ ነበር ብለው ያስተማሩኝዕውነት እንደሆነ በሕይወት እያለሁ ይኸው ተረዳሁኝ::አላቂነታችው አልታይ ብሏቸው በትዕቢት ቀጠሉ ግፉን ሰቆቃውንእንዴት ቢንቁን ነው?.…እየጠሉ ገዙን ደንቆሮ አድርገውን::ፈጣሪን በማመን በደም ባጥንታቸው ወያኔን ሊያባሩያልሰማህ ከሆነ ከተነሱ ባጁ ሃሞተ ኮስታሮች የማይበገሩ::ጥቂቶች ቢሆኑም ሕዝባቸውን አምነው ፈተናውን አልፈውሳይንበረከኩ ጥርት ባለ ራዕይ ባላማ ታጅበውከፈጣሪ ታዟል የነፃነት ቀንዲል ሊያበሩ ከፍ አርገው::እንደ እግዚአብሔርም ሕያው ነኝ ሁሉን አደርጋለሁሕዝብ እንዲገዛልኝ የፈጣሪ ጥበብ ይኸው ይዣታለሁእያለ ቀባጥሮ እምብዛም አይቆይም እንደ ጉም ይበናልበእርሱ መቃብዕር ላይ ጥበብም ጉልበትም የሕዝቡ ይሆናል::መኖር መደምሰስም በእኔ ፈቃድ ነው ሲልመነሻውን ሳያውቅ የፈጣሪን ጥበብ የያዛት ሲመስልምንድነው ዝምታው ከሕዝብ ጋር ሆነን ዘግ ማድረግ ስንችልጤና የሚገኘው መዝምዘን ሰርስረን ገርስሰን ስንጥል:: |
IF
Carter G. Woodson |
Poem from Lemelm Tsegaw My Brother…
|
Letter from Ethiopian Women living in SouthAfrica
10/10/2006 ከደቡብ አፍሪካ ዘውዲቱ መንገሻ ነን ! |